ሰላምና ፍቅር

ሰላምና ፍቅር Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ሰላምና ፍቅር, Addis Ababa.
(1)

26/06/2026

ከረጅም ጊዜ በኋላ ድምጻዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) ለሚዲያ ከእህቷ ዘማሪት ሶፊያ ሽባባው ጋር ቀርባለች።

25/06/2026

በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተጋራ የሚገኘውና የብዙዎችን ልብ የነካው ይህ አጭር ቪዲዮ፣ ማዕዶት የምትባል የ10 ዓመት እምቡጥ ሕፃን በካንሰር ሕመም ውስጥ ሆና የምታሳየውን አስደናቂ ጥን...
25/06/2026

በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተጋራ የሚገኘውና የብዙዎችን ልብ የነካው ይህ አጭር ቪዲዮ፣ ማዕዶት የምትባል የ10 ዓመት እምቡጥ ሕፃን በካንሰር ሕመም ውስጥ ሆና የምታሳየውን አስደናቂ ጥንካሬ፣ ጽናትና መንፈሳዊ ብርታት በግልጽ ያሳያል። ማዕዶት በቪዲዮው ላይ “የካንሰር ሕመምተኛ ነኝ” በማለት እያለፈችበት ያለውን እጅግ ከባድ የሕይወት ፈተና በታላቅ መረጋጋትና በፈገግታ ትናገራለች።

አንዳንድ ቀናት በጣም አስቸጋሪና ከባድ እንደሚሆኑባት፣ ሕመሙ ከፍተኛ ሥቃይ እንደሚያመጣባት እንዲሁም ትምህርት ቤት ያሉ ጓደኞቿንና አፍቃሪ ቤተሰቦቿን በጣም እንደምትናፍቅ ብትገልጽም፣ አሁንም ድረስ እጅ ሳትሰጥ በጽናትና በደስታ እየታገለች መሆኗን ስትመሰክር የምታሳየው አቀራረብ ለማንኛውም ሰው ትልቅ መነሳሳትን የሚሰጥ ነው።
ማርዶት ምንም እንኳ የሕክምናውን ሂደትና የሚያስከትለውን አካላዊ ጫና በለጋ ዕድሜዋ ብታስተናግድም፣ ለፈጣሪ ያላትን ጥልቅ ምስጋናና እምነት ግን ቅንጣት ታህል አልቀነሰችም።

“እስከምድን ድረስ ተስፋ አልቆርጥም፣ ሁሉም ነገር በፈጣሪ ቸርነት ድል ይሆናል” የምትለው ይህች ታናሽ ጀግና፣ በታላቅ የሕይወት ውጣ ውረድና ሕመም ውስጥ ለሚገኙ ሌሎች ሰዎች ሁሉ እጅግ አነቃቂና ልብን የሚያጠነክር መልዕክት አስተላልፋለች። ማንም ሰው በችግሩ ወቅት ብቻውን እንዳልሆነ እንዲያስብ፣ ተስፋ ሳይቆርጥ በትናንሽ እርምጃዎችም ቢሆን ወደፊት መጓዙን እንዲቀጥልና ፈጣሪ እንደማይረሳው በመግለጽ የሰጠችው አስተያየት የሰውን ልጅ የመኖር ተስፋና ጽናት የሚያድስ ነው። ይህ የሕፃን ማርዶት ታሪክ እኛ ጤናማ ሆነን በትናንሽ የዕለት ተዕለት ችግሮች የምናማርረውን ሰዎች ሁሉ ቆም ብለን ሕይወትን፣ ጤናንና የተሰጠንን ጸጋ በታላቅ ምስጋና እንድንመለከት የሚያስገድድ እውነተኛ የተስፋ መማሪያ ነው።

 #ካሙዙ ካሳ የንዋይ ደበበን አልበም ከልክሏል**************************************አንጋፋው ድምፃዊ ንዋይ ደበበ ከአሜሪካን ሀገር ጀምሮ ስጠበብ የነበራቸውን ድርሰቶች ...
25/06/2026

#ካሙዙ ካሳ የንዋይ ደበበን አልበም ከልክሏል
**************************************
አንጋፋው ድምፃዊ ንዋይ ደበበ ከአሜሪካን ሀገር ጀምሮ ስጠበብ የነበራቸውን ድርሰቶች አብዛኛውን ካሙዙ ካሳ ስቱድዮ ሰርቶ ቢጨርስም ማስተሩን መከልከሉ ገልጿል ንዋይም አክሎ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረድልኝ እያለ ነዉ ከዚህም ባሻጋር ዉድ አድናቂዎቼ አልበም ለህዝብ ያለማቅረቤ ምክንያትም ካሙዙ ካሳ እንደሆነ ዕወቁልኝ ሲል አምኖ መከዳቱን እያሳወቀ ይገኛል።መቼም የማንሰማዉ ጉድ የለም።

https://youtu.be/cBzbFv0VtNk?si=SVAzx6GlhbE0LlwM

25/06/2026
አስደሳች የምስራች፡ በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባት የነበረችው ለይላ ኑርሰቦ ወደ ሀገሯ ልትመለስ ነው::”በሳውዲ አረቢያ እስር ቤት የሞት ፍርድ ተፈርዶባት ለበርካታ ዓመታት በአስቸጋ...
25/06/2026

አስደሳች የምስራች፡ በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባት የነበረችው ለይላ ኑርሰቦ ወደ ሀገሯ ልትመለስ ነው::”

በሳውዲ አረቢያ እስር ቤት የሞት ፍርድ ተፈርዶባት ለበርካታ ዓመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በእስር ላይ የቆየችው ኢትዮጵያዊቷ ለይላ ኑርሰቦ፣ ወደ እናት ሀገሯ የምትመለስበት አስደሳች እና እፎይታን የሚሰጥ መረጃ ተሰምቷል።

የተገኘው ወቅታዊ መረጃ እንደሚያመለክተው፦

* እህት ለይላ ኑርሰቦ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ የሚያስፈልገውን የበረራ ፎርም ሙሉ በሙሉ ሞልታ አጠናቃለች።

* የፊታችን ሰኞ (ኢንሻ አሏህ) ወደ ሀገሯ የምታደርገውን ጉዞ ለመጀመር ትላንት ወደ በረራ ማቆያ ክፍል (Transit/Depredation Center) መዛወሯ ተረጋግጧል።

ይህ መረጃ ለዓመታት በትካዜና በዕንባ ውስጥ ለነበሩት ቤተሰቦቿ፣ እንዲሁም ጉዳዩን በትኩረት ለሚከታተሉ ወገኖች ሁሉ ትልቅ የደስታ የምስራች ሆኗል።

ፈጣሪ (አሏህ) የጀመረችውን የነጻነት ጉዞ በስኬት አጠናቆ፣ በሰላምና በጤና ለሀገር ምድሯና ለቤተሰቦቿ ያብቃት!



መረጃው የሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውስር ሲሆን፣ ጉርሻዎችም ከሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውስር ጋር ተነጋግረናል።

እንዲሁም የለይላ ወንድም፦ «እህቴ ለይላ ለበረራ ዝግጁ ሆናለች፤ በነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ ትገባለች ብለው ደውለውልኛል» ብሏል።"ኢንሻ አሏህ ።

Via ጉርሻ Page

25/06/2026

አይ ፍቅር😢🥹🥹

ከካምፓስ ወደ እንግልት፡ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አስለቃሽ የቤት ጉዞድሬዳዋ፣ ኢትዮጵያ — የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዓመት ትምህርታቸውን አጠናቀው ለዕረፍት ...
25/06/2026

ከካምፓስ ወደ እንግልት፡ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አስለቃሽ የቤት ጉዞ

ድሬዳዋ፣ ኢትዮጵያ — የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዓመት ትምህርታቸውን አጠናቀው ለዕረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው ለማምራት ያደረጉት ጉዞ፣ ወደ አስከፊ የዘረፋ፣ የድብደባ እና የውርደት መድረክ የተቀየረበት አሳዛኝ ክስተት ተፈጽሟል።

ሰኔ 16 ቀን ቁጥራቸው 72 የሚሆኑ ተማሪዎች ፈቃድ ወስደውና ገንዘብ አዋጥተው የኮንትራት መኪና በመያዝ ነበር ጉዟቸውን የጀመሩት።

በዩኒቨርሲቲው ካምፓስ ግቢ ውስጥ ዕቃዎቻቸው ተፈትሸው፣ የፈቃድ ወረቀት ተጽፎላቸውና መታወቂያቸውን (ID) ይዘው ምንም ዓይነት እንግልት እንዳይገጥማቸው በጥንቃቄ ሌሊት 8 ሰዓት ላይ ተነሱ። ሆኖም ግን በመንገድ ላይ የሚጠብቃቸውን መከራ ፈጽሞ አልገመቱም ነበር።

ማለዳ 2 ሰዓት ተኩል ላይ የጭሮ መግቢያ በሆነው አባረካቴ' ለሚባለው ልዩ ቦታ ደረሱ። በኬላው ላይ የነበሩት አካላት መኪናውን ያስቆሙ ሲሆን፣ ተማሪዎቹ ሕጋዊ የፈቃድ ወረቀታቸውንና የዩኒቨርሲቲ መታወቂያቸውን ቢያሳዩም የሚሰማቸው ሰው አጡ።
የጸጥታ አካላቱ የተማሪዎቹን ማስረጃዎች ወደ ጎን በመተው፣ ተማሪዎች ለወላጆቻቸው የገዟቸውን ንብረቶች መዝረፍ ጀመሩ።

"አንዳንድ ተማሪዎች ለቤተሰቦቻቸው፣ ለአባታቸውና ለእናታቸው የገዟቸውን አዳዲስ ብርድ ልብሶች ከመኪናው ላይ እየወረወሩ በጠራራ ጸሀይ ዘረፉን። እኛ ምንም የማናውቅ ንጹሐን ተማሪዎች ልክ እንደ ኮንትሮባንድ ነጋዴ ተቆጥረን ምን እንደምናደርግና ምን እንደምናተው ግራ ገባን፤ በለቅሶ እና በንዴት ልባችን አርሮ አልፈን ሄድን።" ሲል አንዱ ተማሪ በምሬት ይናገራል።

በዚህ ኬላ ላይ ለሁለት ሰዓት ተኩል ሙሉ ተማሪዎቹን በማቆም ሲያፌዙባቸው የቆዩ ሲሆን፣ ድርጊቱ በዕቃ መቀማት ብቻ አላበቃም፦

* ሁለት ተማሪዎች በዱላ ክፉኛ ተደበደቡ።
* ሦስት ተማሪዎች ደግሞ ተደብድበው ከሾፌሩ ጋር አብረው ታስረው ተወሰዱ።
* ተማሪዎቹ ለከፍተኛው የሀገሪቱ የጸጥታ አካል ለፌደራል ፖሊስ አብረው ቢጮሁም፣ ፖሊሶቹም ጭምር ከፈታሾቹ ጋር በመሆን ተማሪዎቹን እንደመቷቸው ተገልጿል።

የተማሪዎቹ ሰቆቃ በዚህ አላበቃም፤ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ አዋሽ ኬላ ሲደርሱ የገጠማቸው ነገር በገዛ ሀገራቸው መኖራቸውን ጭራሽ የሚያስረሳ ነበር።

ከመኪናው በላይ የተጫኑት የተማሪዎች ሻንጣዎች በሙሉ አንድ በአንድ እየተፈተሹ ወደ መሬት ተወረወሩ። ተማሪዎቹ በሕግ እዩልን፣ ዕቃችንን አታበላሹብን በማለት ሲማጸኑ በጥፊና በዱላ እየተመቱ በአስገዳጅ ሁኔታ በሜዳ ላይ እንዲንበረከኩ ተደረገ።

"በዚያች ቅጽበት ራሳችንን ሊቢያ ውስጥ እገታ ላይ የወደቅን ያህል ተሰማን። እርስ በእርሳችን እየተያየን የሰው ሀገር ተመኘን፣ ራሳችንንም ጠላን" ይላል መልዕክቱን ያጋራው ተማሪ።

ይህ ተማሪ ገና ወደ ዩኒቨርሲቲ ሳይሄድ ቤተሰቦቹ የገዙለትን አንድ ሱሪ እና ሁለት ቲሸርት እንደቀሙት ገልጿል። "ይህ እኮ የለበስኩት እና ያለፈው ዓመት ልብሴ ነው" ብሎ ቢጮህም የተሰጠው ምላሽ *"ሂድ አንተ ሌባ፣ ቁጭ በል እዚያ!"* የሚል ስድብና ማዋረድ ነበር።

በዚህ አሰቃቂ ድርጊት ውስጥ እጅግ ልብ ሰባሪው ክስተት የተፈጸመው በአንዲት ሴት ተማሪ ላይ ነው። የያዘችውን ዕቃ ሁሉ ሲቀሟት "ልብሴን ስጡኝ፣ ካልሆነ ግን ግደሉኝ" በማለት እምቢተኝነቷን ብታሳይም፣ የጸጥታ አካላቱ ዕቃዋን ለመመለስ ፍቃደኛ አልሆኑም።

በመጨረሻም የኮንትራት መኪናው እሷን በኬላው ላይ ጥሏት እንዲሄድ በመገደዱ፣ ጓደኞቿ በለቅሶና በጭንቀት እዚያው ጥለዋት ለመሄድ ተገደዋል።

ይህ በእነዚህ ወጣት ተማሪዎች ላይ የተፈጸመው ድርጊት እጅግ አስነዋሪና ትልቅ ውርደት መሆኑን ተማሪዎቹ በከፍተኛ ቅሬታ ይገልጻሉ። ክስተቱ በሀገሪቱ ያለውን የፍትሕ መጓደል እና ድርብ መስፈርት በግልጽ ያሳየ ነው።

በውነቱ ያማል እጅግ ክፉኛ በደል ደርሶብናል ሲሉ እንዲሁም ለሚመለከታቸው አካላት እና ለፌደራል ፖሊስ የቀረበ አስቸኳይ የቅሬታና የምርመራ ጥሪ አቅርበዋል

* በአባረካቴ እና በአዋሽ ኬላዎች ላይ በተማሪዎች ላይ አካላዊ ጥቃት የፈጸሙትን፣ ንብረቶቻቸውን የዘረፉትን እና ያሰሯቸውን የጸጥታ አባላት በአስቸኳይ እንዲያጣሩ፤ ጥፋተኞችንም ለሕግ እንዲያቀርቡ።

* ለድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ከተቋማችሁ በሕጋዊ መንገድ ተፈትሸውና የፈቃድ ወረቀት ተሰጥቷቸው የወጡትን ተማሪዎች ደኅንነት የመከታተልና መብታቸውን የማስከበር ኃላፊነት ስላለባችሁ፣ ከተያዙት የጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር የተማሪዎቹ ንብረት እንዲመለስና የታሰሩትም እንዲፈቱ ግፊት እንድታደርጉ።

የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ወጣት ተማሪዎች በገዛ ሀገራቸው መሄጃ አጥተው ሊለቅሱ፣ ሊደበደቡና ሊዋረዱ አይገባም! ሲል በደል የደረሰባቸው ተማሪዎች አስረድተዋል::

Via የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎ

24/06/2026

የቀጠናው ስጋት 😂😂 እነ ፋዘር እየተፍታቱ ነው ይመቻቹ🤗😀

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰላምና ፍቅር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share