DHaabbata leenjii konkolaachistoota IRKO እርኮ የ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም

  • Home
  • Ethiopia
  • Adama
  • DHaabbata leenjii konkolaachistoota IRKO እርኮ የ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም

DHaabbata leenjii konkolaachistoota IRKO እርኮ የ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም Number one school

18/04/2023

የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ 27 ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ከዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች ለተመረቁ ሥራ አጥ ወጣቶች አበረከተ
***********************

የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ የዘርፉን ባለሃብቶች በማስተባበር የገዛቸውን 27 ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ከዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች ለተመረቁ ሥራ አጥ ወጣቶች አበርክቷል።

ኤጀንሲው ከአሽከርካሪ የሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች የተመረቁ እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ 840 ተማሪዎችን በነፃ የአሽከርካሪነት ሙያ በማሰልጠን አስመርቋል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ጀማል ከድር እንደገለጹት፣ ኤጀንሲው የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን ከማሳለጥ ጎን ለጎን ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተማሪዎች የሥራ ዕድል አግኝተው ጥሪት የሚያፈሩበትን ፕሮግራም በመቅረጽ እየሠራ ይገኛል።

በዚህም ከአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በመተባበር 840 የሚሆኑ ተመራቂዎችን በነፃ አሰልጥኖ የአሽከርካሪ ሙያ ፍቃድ እንዲያገኙ አድርጓል ብለዋል።

በዚህ ነፃ የስልጠና መርሐ-ግብር ሰልጥነው የአሽከርካሪነት ሙያ ፍቃድ ካገኙት ውስጥ 540 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ኤጀንሲው የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማቱን በማስተባበር ከ9.2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 27 ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ በመግዛት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 54 ሥራ አጥ ወጣቶች ማበርከቱም ተገልጿል።

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld/
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/EBCNEWSNOW
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የቲክቶክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.tiktok.com/

31/03/2023
Telegram
03/12/2022

Telegram

Number one Driving training centers

29/11/2022

አዲስ ቆጣሪ ለማግኘት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ሲመጡ እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎችን ያሟሉ
*******************
ተቋማችን አዲስ ቆጣሪ የሚፈልጉ ደንበኞችን በቀላሉ መገልገል እንዲችሉ በቅርቡ አዲስ መመሪያ አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል፡፡ እርሶም አዲስ ቆጣሪ ለማግኘት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ሲመጡ ቀጣይ የተገለፁትን ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟሉ እንጠይቃለን፡፡

የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ /Single Phase Meter/ ለማግኘት፡-

• የአመልካቹ የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ፣
• አንድ ጉርድ ፎቶ /3 በ 4 የሆነ/፣
• የኪራይ ቤት ከሆነ ከባለቤቱ የተሰጠ የስምምነት ደብዳቤ፣
• ለኃይል ማሻሻያ ወይም ለተጨማሪ ቆጣሪ ከሆነ የኤሌክትሪክ ፍጆታ የመጨረሻ ክፍያ ደረሰኝ፣
• ጥያቄው ለሽርክና ማህበር ከሆነ በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የሽርክና ማረጋገጫ ሰነድ ኮፒ፤

• የኃይል ጥያቄው በመንግስት ለሚተዳደሩ ቤቶችና ቦታዎች ከሆነ፡-

 የኃይል ጥያቂውን ያቀረበው ቤቱን በመንግስት ስም የተዋዋለ ተከራይ ከሆነ በሚመለከተው የመንግስት አካል ፍቀድ ማግኘት እና ማንነቱን የሚገልፅ መታወቂያ ሲያቀርብ አገልግሎቱ የሚፈቀድለት ሲሆን፤ ማንኛውም ኃላፊነት ቤቱን የሚያስተዳድረው የመንግስት አካል ይሆናል፡፡
 የመንግስት /የቀበሌ ቤት/ ተከራይ የኪራይ ውል አያይዞ ሲያቀርብ አገልግሎቱን በተከራዩ ስም ሊያገኝ ይችላል፡፡ ነገር ግን ሙሉ ኃላፊነት የተከራዩ ይሆናል፡፡

• የኃይል ጥያቄው ኃላፊነቱ ለተወሰነ የግል ድርጅት ከሆነ ከላይ በተራ ቁጥር የተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎች እንዳሉ ሆኖ የድርጅቱ የምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የድርጅቱን ዋና ስራ አስኪያጅ ማንነትን የሚገልፅ መታወቂያ፣

• ኢንስፔክሽን /ማስገመቻ ለነጠላ ፌዝ 90 ብር ይከፈላል፡፡

የሶስት ፌዝ ቆጣሪ /Three Phase Meter/ ለማግኘት፡-

• የኃይል ጥያቄው ከ14 ኪሎ ዋት እና በላይ ከሆነ ከላይ ለነጠላ ፌዝ አገልግሎት ከተጠቀሱት ማስረጃዎች በተጨማሪ በኤሌክትሪክ ነክ ሥራዎች ፈቃድ ባለው ተቋራጭ የተሰራ የኤሌክትሪክ ዲዛይን ፕላን ማቅረብ ይጠበቃል፣

• አገልግልቱን ለመስጠት ለሚከናወኑ የኢንስፔክሽን እና የማስገመቻ ክፍያዎች (በየጊዜው የሚደረገው የዋጋ ክለሳ እንደተጠበቀ ሆኖ፣

 ለባለ ሶስት ፌዝ ቆጣሪ 300 ብር፣
 ከ24 ኪሎ ዋት እስከ 120 ኪሎ ዋት 500 ብር፣
 ከ121 ኪሎ ዋት እስከ 1 ሜጋ ዋት 5000 ብር፣
 ከ 1 ሜጋ ዋት በላይ 10 ሺህ ብር ብር የሚከፈል ይሆናል፡፡

በመሆኑም ማንኛውም አዲስ ቆጣሪ የሚፈልግ ደንበኛ ከላይ በተጠቀሱት መስፈርቶች ብቻ አገልግሎቱን የምሰጥ ሲሆን፤ ከዚህ ውጪ በአቋራጭ ቆጣሪ እናስገባለን ከሚሉ ደላሎችና ግለሰቦች እንዲሁም ከሌሎች ብልሹ አሰራሮች ራሳችሁን እንድትጠብቁ በዚህ አጋጣሚ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

17/11/2022

Address

Gadaa
Adama

Telephone

+251919622140

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DHaabbata leenjii konkolaachistoota IRKO እርኮ የ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category