27/12/2025
#ይነበብ
https://www.facebook.com/share/1BATyi7tiD/
‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ለውጥ እና ሪፎርምን ተከትሎ፤ የተሟላ የተሽከርካሪ መሠረታዊ ሰነዶችን አሟልተው ሳያስረክቡ፣ የተሽከርካሪ ገዥዎችን ወደ ተቋማችን የሚልኩ እንዲሁም ጉዳይ አስፈፃሚን በመመደብ ከተገልጋይ ተጨማሪ ክፍያን የሚቀበሉ አስመጪዎችን ከነገ ታሕሳስ 18/2018 ጀምሮ በእኛ ተቋም አገልግሎት እንዳያገኙ የምናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
በመሆኑም ከዛሬ ጀምሮ ሁሉም የተሽከርካሪ አስመጪዎች፣ ለገዥዎች የተሟላ የተሽከርካሪ መሠረታዊ ሰነዶችን በመስጠት፣ ወደ እኛ ተቋም መጥተው ያለ እናንተ ጉዳይ አስፈፃሚ፣ ያለ እንግልት እና ውጣ ውረድ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ መረጃ እንድትሰጡ በጥብቅ እናሳስባለን።